top of page
Search

ሰበር ዜና

ሰበር ዜና

--

የአግዛዙ ሰራዊት በደላንታ ተደመሰሰ !

ኢትዮ ሰገነት ሚዲያ

ህዳር 7/ 2018 ዓ/ም


በደላንታ ዙሪያ የዐብይ አህመድ አገዛዝ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊ በሻለቃ አመራሩ ላይ ጥቃት ሲፈፀምበት በርካታ እግረኛ ሰራዊቱ ደግሞ ሙትና ቁስለኛ መሆኑ ተገለጸ።


አፋብኃ ምስርቅ አማራ ቀጠና ሚኒሊክ ዕዝ የደጋው መብረቅ ኮር ፅናት ክፍለ ጦር የአገዛዙን ሻለቃ አመራር ከባድ ቁስለኛ በማድረግና ከሶስት ጓድ በላይ እግረኛ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ማስምዝገቡን የኢትዮ ሰገነት ምንጮች ገለጹ።


ልዩ ስሙ ዚሃ ተብሎ በሚጠራው ቦታ በፋብሃ ምኒልክ ዕዝ ልጅ እያሱ ኮር በከፍተኛ የውጊያ ጥበብ የደረሰበትን ከፍተኛ ጥቃት መቋቋም ያቃተው የአገዛዙ ሰራዊት እግሬ አውጭኝ ብሎ ወደ ደላንታ ወረዳ መፈርጠጡን የግንባር መረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።


የአገዛዙ ሰራዊት ተበትኖ ሲሸሽ የምኒልክ ዕዝ ፅናት ክፍለ ጦር መክት ሻለቃ 3ኛ ሻምበል ባደረጉት የደፈጣ ኦፕሬሽን በርካታ የጥላት ሰራዊት መደምሰሱን የግንባር መረጃ ምንጮቻችን አክለው ገልጸዋል።


ይህ በእንዲህ እንዳለ አምባሰል ወረዳ ውስጥ ባትሪ በተባለ ቦታ ላይ በተደረገ ደፈጣ ሻለቃ መሪው ከባድ ቁስለኛ ሲሆን፣7(ሰባት) የጥላት ሰራዊት ሲደመሰሱ አስራ አራቱ ከባድ ቁስለኛ መሆናቸውም ተረግስግጦአል።


ኢትዮ ሰገነት ሚዲያ

ህዳር 7/2018 ዓ.ም

 
 
 

Comments


bottom of page